News

Politics

History

Latest Release

Friday, March 20, 2020


Thursday, November 12, 2015

*“እምረሐብ ይኄይስ ኮይናት (ከረሐብ ጦርነት ይሻላል)”* (፩)




*“እምረሐብ ይኄይስ ኮይናት (ከረሐብ ጦርነት ይሻላል)”* (፩)
(ሱራፌል ሐቢብ)
ሰው ለመብላት ባይኖርም ፤ ለመኖር ግን  መብላት ግዱ ነው፤ የማንኛውም ፍጡር ህልውና ከመብላት እና ካለመብላት ጋር የተቆራኘ ነው፤ የበላ ይኖራል፣ ያልበላ ደግሞ ይራባል ፤የተራበ ደግሞ ርሐቡን ማስታገሻ ካላገኘ መኖሩ ያከትማል፤ በግልፅ ቋንቋ ይሞታል፡፡ ረሐብ ጊዜ አይሰጥም ፣ ከመብልም ውጪ ማርከሻ የለውም፡፡  አንድ ግለሰብ የሚበላው አጥቶ ቢቸገርና በጠኔ ቢሞት፡- “ሰርቶ አይበላም ነበር”፣ “ሰነፍ” ፣ “ለአንድ ራሱ መሆን አቅቶት ነው” እና የመሳሰሉት ዓይነት የወቀሳ ትችቶች ከመቃብሩ በላይ ሊሰሙ ይችሉ ይሆናል፤ ነገር ግን አንዲህ አንደአሁኑ 15 ሚሊዮን ሕዝብ በረሐብ አለንጋ ሲገረፍ፤ ለሞትና፣ ለስደት ሲዳረግ ማን ነው ተወቃሹ? ማንስ ነው ለዚህ ችግር መስፋፋት ተጠያቂ? ማን ነው እርሱ ኃላፊነቱን ሊወስድ የሚገባው?
የረሐቡ ሰበብ  በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በተከሰተ የዝናብ እጥረት ይሁን በሌላ፤ አንዴት አስቀድሞ ከተነገረን ለችግሩ ተጋለጭ ከሆነው 2.5 ሚሊዮነ ሕዝብ መጠን አለት ተለት በማሻቀብ ዛሬ ላይ 15 ሚሊዮን ደረሰ? ችግሩስ ለምንና አንዴት በጊዜ ሂደት የሚያካልለውን የሀገሪቱን የቆዳ ስፋት መጠን እያሳደገ መጣ?
አንዲህ ሐገር በሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎቿ በረሐብ ችግር ሲናጡ፣ ሲሞቱና ሲሰዳዱ፤ ተጠያቂው፣ ተወቃሹና ኃላፊነቱን ሊወስድ የሚገባው ሀገሬውን የሚያሰተዳድረው መንግስት አንጂ በረሐቡ ጅማሬ ወቅት ከብቶችን ውሀ ወዳለበት ስፍራ አላንቀሰቀሱም  ተብለው የተወቀሱ ምስኪን የረሐቡ ገፈት ቀማሾች የሆኑ አረኞች አይደሉም፤  ችግሩ የሚፈታው  “ራሳችንን በምግብ ችለናል፣ ችግሮቿን በራሷ አቅም የምትፈታ ኢትዮጵያ ተገንብታለች፣ ለርዳታ የሚንሯሯጥበት ጊዜ አልፏል፣ እንኳን እኛ አውስትራሊያ እና ካሊፎርኒያ በድርቅ እየተሰቃዩ ነው……………ወዘተ” በተሰኙ ተራ ዲሰኩሮችና ውሸቶች ሳይሆን የሚናገሩትን በመስራትና በፍጥነት ለችግሩ መፍትሔ በማፈላለግ ነው፡፡ እናንት ገዢዎች ሆይ፡-  ረሐብ ጊዜ አይሰጥም በመሆኑም በተራ ዲሰኩርና ሐሰት ጊዜን ከማባከንና አንዲህ አንደአሁኑ ችግሩን ከማባባስ ረጂዎችንና ሕዝቡን ያሳተፈ መፍተሔ ፍለጋ ላይ መሰማራቱ  ይበጃችኋል፡፡ በተራ ዲሰኩር የመፍተሔውን ጊዜ አያባከናችሁ ለረሐብ ችግርና አርሱን ተከትሎ ለሚከሰት የሞት አደጋ የሚጋለጠውን የወገኔን ቁጥር በየሳምንቱ በእጥፍ አታሳድጉት!! የዘመናት ውሸታችሁ ዓይኑን አፍጦ በመጣ ትልቅ አውነት ተጋልጧልና! ከእንግዲህስ ምን ማለት ይቻላችኋል??!!
“ከረሐብ ጦርነት ይሻላል” አንዲል ቅዱስ መፅሐፍ የረሐብን ኃያልነት እና ፋታ አይሰጤነት የሚያጤን ሕሊና ሊኖራችሁ አንደሚገባ ሊነገራችሁ አይገባም!!!
   

Monday, November 9, 2015

ያንድ ሰንጋ ትርጉም በሁለት ልኳንዳ ቤቶች ካራ

.
ይኽ በስዕሉ ላይ የምትመለከቱት የስጋ ተራራ የተሰኘ ሰንጋ የትውልድ መንደሩ ከወደ ሐረር ነው፡፡ አሳዳጊው ሐረር ውስጥ የምትገኝ አንድ የገጠር ቀበሌ መስጂድ ሼህ የሆኑት ሀጂ እንድሪስ ናቸው፡፡የዚህ መልከኛ ሻኛም ሰንጋ የዘር ሀረግ ሲመዘዝ እንደሚከተለው ነው፡፡የእናቱ የትውልድ ሀረግ የከብት አርቢ ከሆነው ስመጥር የአፋር ክልል ተወላጅ ከብቶች ዘር ግንድ ከሆኑትና የወተት ምንጭ እየተባሉ ከሚንቆለጳጰሱት ያርብቶ አደር ከብቶች ወገን ናት፡፡
 

አባቱ በመንደሪቷ ውስጥ አለ የሚባል የከብት በረት እየገለበጠ የመንደሪቷን ልጃገረድና ድርስ ጊደሮች ሚደፍር ሽንጣምና ቁመተ መለሎው፤ አሳዳጊው ቄስ ሞገሴ አፄ-በጉልበቱ እያሉ ሚጠሩት ኮርማ ነው፡፡ አባቱ አፄ-በጉልበቱ መንደሬው ዘሩን ፍለጋ ሰርክ ድርስ ጊደሩን እየያዘ ቄስ ሞገሴን ደጅ ሚጠናለት፤በቀን ከሶስት ያላነሱ ጊደሮችን አንገት ጠምዘው በግድ ሲያስጠቁት ደከመኝ የማያውቅ ወስዋሽ ጀግና ኮርማ ነበር፡፡አብዛኞቹ የመንደሪቷ ላምና ሰንጋዎች የዚሁ በውድም በግድም ጊደሮች ላይ ጥቃት አድራሽ የሆነው(አጥቂው) አፄ-በጉልበቱ የተሰኘው አባቱ አብራክ ክፋይ ናቸው በዚህም ካብዛኛው የመንደሪቷ ከብቶች ጋር የስጋ ዝምድና አለው ያባት ወገን እህትና ወንድሞቹ ናቸው፡፡
ቄስ ሞገሴና ሀጂ እንድሪስም ቢሆኑ ካንድ መንደር ኗሪነታቸውም ባለፈ ካንድ ሸንጎ የሚቀመጡ፣የተጣላን የሚያስታርቁ ሀገር ሚያከብራቸው ሽማግሎችና የልብ ወዳጅም ናቸው፡፡ ሀጂ እንድሪስ የግተ ለምለም ዘር የሆነችው ጊደራቸው ላቅመ ግንኙነት ደርሳ ኖሮ እብልቷ ፍም ሲመስል የታሰረችበትን ገመድ ልትበጥስ በረቱን እያመሰች ብታስቸግራቸው...እምቧ!!... እምቧ!! እያለች... በምቧቧ ከረዮዋ እረፍት ብትነሳቸው ረመዳን በወጣ በሳምንቱ ባንዱ ለት ማልደው ቄስ ሞገሴ ጋር ይዘዋት ሄደው ለቀበኛው ኮርማ አፄ-በጉልበቱ ቁርስ አስደረጓት፡፡ ይኽ ስጋም የስጋ ተራራ ለመባል የበቃው ሰንጋም ያን ዕለት ተፀነሰ፡፡
ገና በናቱ ማህፀን እያለ ያለቅጥ እድገት ያመጣው ፅንስ እናቱ በርግዝና ዘመኗ ከቦታ ወደ ቦታ እንዳትንቀሳቀስ ከልክሏት ባለቤቱንም ሆነ መንደርተኛውን ስጋት ውስጥ ጥሎ ነበር፡፡የናቱ የርጉዝ ሆዷ አወጣጠር ከመንታም በላይ እንደያዘች ያያት ሰው ሁሉ ጥርጣሬ አልነበረውም፡፡ግዜው ደርሶ ከረጅም ምጥ በኋላ ጥጃው ሲወለድ ግን መንደርተኛው እንዳሰበው መንቶች ሆነው አልተገኙም፡፡ ይልቁንም ገና በማለዳው የስጋ ሰንጋነቱ ውልውል ውስጥ የማይገባው አንዱ ጥጃ የሁለት ጥጆችን ግዝፈት የያዘ ጥጃ ሆኖ ተወለደ እንጂ፡፡የዚህን ገዛፋ ጥጃ መወለድ ዜናን፤ሀጂ እንድሪስ በወተት እንደምታራጫቸው ተስፋ የጣሉባት ዘረ ግተ ለምለም ጊደራቸው በሰላም መገላገሏን የሰማ ሀገሬ ሁላ ባገሩ ደንብ መሰረት የእንኳን ደስ አሎት ምኞቱን አጎረፈላቸው፡፡
ሀጂ እንድሪስም የወተት ጌታ ለመሆን ያበቃቸውን አላህ በደስታ ተሞልተው አመሰገኑ ላዲስ ውልድ ጥጃቸውም የስጋ ተራራ ሲሉ ስም አወጡለት፡፡ ከልጅነት እስከ ወይፈንነት ሲለጥቅም ላቅመ ሰንጋነት እስከበቃበት ዕድሜው ድረስ እንደ ስሙ የስጋ ተራራ እስኪያክል እየቀለቡ አሳደጉት፡፡የዚህ የስጋ ተራራ የሚመስል ሰንጋ ታሪክም ከሀረር እየተሳበ አዲስ አበቤውን በሞንሟና ስጋ አቅርቦታቸው ጉድ የሚያስብሉት ልኳንዳ አራጆች እነ ጭንቅሎ፣ ጊርጊሮና ቢላል ጆሮ ደረሰ፡፡
የበሬ ነጋዴው፣የደላላው፣የባለልኳንዳው ካልሽጡልን ውትወታ ሀጂ እንድሪስን መቀመጫ ነሳቸው፡፡ መጀመሪያ ሰሞን በእንቢታቸው ቢፀኑም “ድሮስ ገበሬ ከብት ሚያረባና ሚያደልብ ሁነኛ ጥቅም ሊያገኝበት እንጂ እበረት አጉረው አይን-አይኑን ቢያዩት ምን ዋጋ አለው!!...ደግሞም አላህ በስተርጅናዎ ደጅዎ ድረስ ያመጣሎትን እርዝቅ(አዱኛ) መግፋት ጡር አለው፡፡አላህ ክፉውን ያርቅልዎ እንጂ እንኳን የከብት የሰው ቋሚ እንደሌለው መቼም እኛ ለርስዎ አንነግሮትም፡፡ ይሄን የመሰለ የስጋ ዳሽን በከብት በሽታ ፍግም ያለ ለት ኋላ የሚተርፍዎ ፀፀት ነው” እያለ ጎረቤት መንደሩ ከምክር ደብልቆ ፍርሃት ቢነዛባቸው ነገሩን አጢነው ለፉክክር ከቀረቡ ተጫራች ልኳንደኞች አንዱ ከቃላቸው አይወጡም ለሚባሉት የልብ ወዳጃቸው እጅ መንሻ ሰጥቶ ላስጀነጀናቸው ለሳቸውም አይናቸውን ማያሹበት ዋጋ አቅርቦ ልባቸውን ላማለለው ለክርስቲያን አራጁ ጊርጊሮ ፤ እንዲሁም አንዱን ከስጋ ተራራው መለስ ያለውን ሌላ ሰንጋቸውን ደግሞ “ይኼን የስጋ ተራራ ለሌላ ሰው አሳልፈው ከሰጡ ወላሂ እቀየሞታለሁ” እያለ ለሞገታቸው ቢላል “አላህ ስጋውን ይባርክላችሁ!!” ብለው መርቀው ሸጡላቸው፡
 መቼም ሰንጋ በቁሙ እያለ ክርስቲያንም ይሁን እስላም ቤት ይደግ ሀይማኖት የለውም፡፡ሰንጋ በቁሙ እያለ ባርባ ቀኑ ክርስትና ተነስቶ ክርስቲያን ሰንጋ ተብሎ ባንገት ክሩ አይለይ?!... አሊያም ባሳዳጊ በባለቤቱ ሐይማኖት ህግ መሰረት ሰልሞ እስላም ሰንጋ ተብሎ መለያ ቆብ አይደፋ?!...መቼም ሰንጋ በቁሙ እያለ እስላሙ ለክርስቲያኑ ፤ክርስቲያኑ ለእስላሙ አልሸጥልህም፣አልገዛህም ላይባባሉ ነገር...
በሞቱ፤ባንገቱ የተሳለ ካራ ካሳረፉ በኋላ ወርችና ዳቢቱን...ሽንጥና ሻኛውን...ታላቅና ታናሹን ...ምላስና ሰንበሩን...ጎድንና ቅልጥሙን...ጉበትና ኩላሊቱን... በካራ ክርስትና ማንሳት፤ባራጁ ካራ ማስለም... ከገደሉ በኋላ ስጋውን ለገዛ ሃሳባችን...በቁሙ ቁልቢን ብለን የሸጥነውን፤ወላሂ ብለን የገዛነውን ሰንጋ ከጣልነው፣ከገፈፍነው፣ከበለትነው በኋላ ብንለያይበት፣የሚበላውን ከወዳቂው አካሉ ነጥለን ...ስጋውን ከቀንድ ና ቆዳው ለይቶ የሚያናጅስ ሐይማኖታዊ የቢስሚላሂና የበስመ-አብ ፅንሰ ሐሳብ፤ያንድ ሰንጋ ትርጉም በሁለት ልኳንዳ ቤቶች ካራ ልዩነት፣በአራጁ ምናባዊ መነባንብ…አራጁ ካራውን በሬው አንገት ላይ በሚሽጥበት ትርጉም የለሽ አቅጣጫ፤በሬውን ለመጣል እኛ በፈጠርነው የሀሳብ ዞን፤ወደ መካ፣ ወደ ምስራቅ አውድቀን በንሰሳው ውድቀትና አወዳደቅ ሃላል፣የተባረከ እያልን በከንቱ ሰዋዊ ሀሳባችን መዋደቅ ትርጉም የለሽ ይሆንብኛል...
የቀንድ ዋንጫውን፣ከቆዳው የተበጀውን ጫማና፣የቆዳ ልብስ ያለልዩነት እየተጠቀምን በስጋው መለያየት የፈለግንበት የክፋት ምርጫችን ሰማያዊነት፣ጀነታዊነት አልታይህ ይለኛል...የሐይማኖትና ሐይማኖተኞች አስተምህሮ ከፍቅርና አብሮነት ይልቅ ለልዩነት ያላቸውን የፀና አቋም አስረጂ ይመስለኛል፡፡ አባ ለሚካዔል ያመት ንግስ ለት ለቅዳሴ ከቤትዋ ሲወጡ ያረጉት መጫሚያዎ ሲረግጡት ቢስሚላሂ!!...ቢስሚላሂ!!...ያ-አላህ!!..ያ-አላህ!! ይላል…ምነው የእስላምና ክርስቲያን ስጋ ሲለዩ …የእስላምና ክርስቲያን ቆዳ መለየት ተሳንዎ?!... ሀጂ ለጁምዓ ለት ስግደት ሲሄዱ ያረጉት መጫሚያዎ ሲረግጡት በስማብ-በወልድ!!...በስማብ-በወልድ!!...ምነው በድንግሊቷ?!...ምነው በኡራኤል!!...ይላል እርስዎስ ቢሆኑ ምነው የእስላምና ክርስቲያን ስጋ ሲለዩ …የእስላምና ክርስቲያን  ቆዳ መለየት ተሳንዎ?!...


ይህቺን ሊንክ ከልከው https://www.facebook.com/kindeta ዘለቅ ብለው ያንብቡኝ!!... እርሶም የመውደጃ ምልክተዋን ተጭነው መውደድ- መዋደድዎን አይርሱ?! ለወዳጅዎም ግብዣ ይላኩ፡፡

Thursday, October 29, 2015

ጭን-ገረድነት፣ውሽምነትናቅምጥነት ባለትንሳዔው ትውፊታችን


#ክንዴነህ ታመነ #Kindeneh Tamene

እንዴት ከረማችሁማ ብዬ ጥሁፌን ልጀምራት አልኩና የኤፍሬም እንዳለ ወግ ልትሆንብኝ ሆነ…የቀኑ ደመናማነት ሀገሩን የጥጥ ማሳ አስመስሎታል….ሰማዩ በተራው ጭጋጋማ ቀለም የተቀባ የሰዓሊ ሸራ ይመስላል… ፀሐይት እንደ አብዮት ልጆቿን ቀርጥፋ ልትበላ አደባባይ የወጣች ነፍጠኛ ትመስላለች ብዬ ልጀምር አሰብኩና በዕውቀቱ ስዩም በሀገራችን ድርሰት ፅሁፎች መቼት ገለጻ ላይ  ያፌዘባት ጥሁፉ ትዝ ብትለኝ … ጥሁፌን እንዴት ብዬ ልጀምራት ይሆን ሀሳብ ተቸንክሬ ሰዐታት ነጎዱ…ኤዲያ ደግሞ እንዴት ልጀምር ብሎ በሃሳብ መንፏቀቅ ምን ይሉት ጅልነት ነው ብዬ ወዲያ ትቼው ልነሳ ሲዳዳኝ አንድ መላ ተዘየደችልኝ…እኔ እስከማውቀው ከሀገራችን ጠሀፍት ውስጥ ጥሁፉን በመፈክር የጀመረ ጠሀፊ ያለም አይመስለኝ …እቺ ያልተበላባት የጥሁፍ መጀመሪያ ስልት ናት…ፈክሮ መጀመር ልዩ ብልሀት ናት…እንግዲህ ግራ እጃችሁን እያነሳችሁ አብረን እንፈክራለን…ዳይ ወደ ፍከራችን !!
የነገደ ሰለሞን ስርወ መንግስታት ያወረሱን የነቃ ማህበረሰብ መለያ የሆነው የጭን-ገረድነት ባህላችንን ጠብቀን ለተተኪው ትውልድ እናስረክባለን!!
ፖለቲካዊ ውሽምነት ለህዳሴያችን መረጋገጥ ዋስትና ነው!!
ህዝባዊ ቅምጥነት የልማታችን ማሳለጫና ሀገራችንን ከፀረ-ልማት ኃይሎች ምንታደግበት የተባበረ ክንዳችን መገለጫ ነው!!
ጭን-ገረድነት፣ውሽምነትና ቅምጥነት ሰፊው ህዝባችን በሀገሩ ፖለቲካ  ውስጥ ያለውን ተሳትፎ የሚያረጋግጥበት የተሞክሮ መድረክ ይሆናል !!
አሁን ከፍከራ ብዛት የዛለ ክንዳችንን ለልማታዊ ሐሳባችን እናውለው፡፡ከዚህ ቀደም  “የአይጦች ግልቢያ” ወይም “ራት ሬስ” ብዬ የጣፍኳትን ጥሁፍ ያነበባችሁ ሰዎች ምን ይዘባርቃል እንዳትሉ በቀደመው ፅሁፌ ለማንሳት የወደድኩት ሃሳብ በሀገራችን ፖለቲካ ውስጥ በተቃውሞ አሊያም ፅንፍ በያዘ ዘርና ዘረኝነትን መሰረት ባደረገ የፖለቲካ አጀንዳቸው ጎራ የለዩ ወገኖችና እንዲሁም (የገዢው ፓርቲ ልሂቃን እንደሚሉት ፖለቲካ ሐይማኖት አይደለም፤ማንኛውም ጥቅሙ የተከበረለት አካል የፓርቲው የተባበረ የኃይል ክንድና የአውራ(ሬ) ፓርቲው ቀጣይ ህልውና መሰረት ይሆናል በሚል ፍልስፍናና ፖለቲካዊ ብልጠት ከጊዜና ከወቅት ጋር እየተሰናሰለ በሚቀረፅ ፖለቲካዊ ስትራቴጂ  ለአዳዲስ አባላት ምልመላ ፓርቲው ከሚሠጠው ትኩረት በላይ የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍልን የጥቅም ተጋሪ በማድረግ ጊዜያዊ ጥቅሙ የተከበረለት በጥቅም የታወረ  ጭፍን ደጋፊ የማበራከት ፖለቲካዊ መሰሪነት ተጋላጭ(ቨልነራበል)የሆነው ክፍልና በጭፍን ደጋፊነት  ጎራ የተሰለፈው ወገንና  የተቃውሞ  ፖለቲካዊ የትግል ጎራ የተበጣጠሰና ከሚያቀራርበው ነገር ይልቅ የሚያራርቅ የብሄርተኝነት አጀንዳቸው  ለገዢው ፓርቲ ዕድሜ ማራዘሚያነት የተቀመመ የዘር ፖለቲካ መርዘኛ  እሳቤ የማስፈፀም አይጣዊ ሚናቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ለማሣየት ያሰበ ነበር፡፡የዚህን ጥሁፍ ሙሉ ሃሳብ ማንበብ ከፈለጉ ወረድ ብለው ገፄን ይመልከቱ፡፡
ለዚህ ፅሁፌ መነሻ የሆነኝ ከአበዋዊ ብሂል፣ባህል ጋር የተሰናሰለ ዘመናዊነት እና ቇቅነት የወለደው ፋሽን አሊያም የመተጣጠፍ አኗኗር ዘይቤ፤ ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ ጭን-ገረዳዊ ፖለቲካዊ ማንነት፤እናቴን ያገባ ሁሉም አባቴ ነው ባይ ውሽማዊ ኢትዮጵያዊ ጠባይ፣ወይ ካለው ተወለድ ወይ ካለው ተጠጋ ሀገርኛ የቅምጥነት አመለካከት ሰዋዊ ስብዕናን ሽባ አድርጎ የሚያስቀር የአመለካከት ልምሻነት ከትውፊት፣ከባህል፣ከሐይማኖት እና ፖለቲካዊ ስርአቶች ጋር ያላቸውን ቁርኝትና የዛሬው ጉራማይሌ ሀገራዊ አመለካከታችን ሰበበ መንስዔ  ይሆናል ያልኩትን ግላዊ ምልከታዬን ማቋደስ ነው፡፡በኔ እምነት ፅንፍ የያዙ ድጋፍና ተቃውሞ ፖለቲካዊ አመለካከቶች ከነጉድፋቸው በምንም መስፈርት ከላይ ካነሳሁት የአመለካከት ልምሻነት ጋር  ለንፅፅር እሚቀርቡ አይደሉም፡፡የሰው ልጅ ለሚያምንበት ነገር፣ለሚያምንበት ዕውነት መቆሙ የሰውነቱ መገለጫ ነው፡፡ዕውነቱና ዕምነቱ እንዲሁም የቆመለት ዓላማ ሀገርና ወገንን ታሳቢ ያደረገ ነው?...የሰፊውን ህዝብ የባህል፣የሐይማኖት፣የብሔር ነፃነት አስጠብቆ ሀገርን በጋራና ባንድነት ሚያራምድ  ነው ዓላማው?በሚለው ጉዳይ ላይ ያለን ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ
በግሌ የትኛውም ግለሰብ ሆነ ቡድን ቆሜለታለሁ የሚለው ፖለቲካዊ አላማ ቅዱስ አሊያም እርኩስ ነው ብለን እምናወድስበትና እምንኮንንበት ሁላችንንም ሊያስማማ የሚችል መስፈሪያ ባይኖረም…ግለሰቡ ወይም ቡድኑ የያዘው መስመር ሰይጣናዊ ይሁን መላዕካዊ፣ቅዱስም ይሁን እርኩስ ፣አጥፊም ሆነ አልሚ ቢያንስ የቆመለት፣የሚቆምለት ዓላማ አለው፤ቢያንስ የሚገድልበትና የሚሞትለት ምክንያት አለው፡፡በተመሳሳይ ከጭፍን ጥላቻና ከጭፍን ደጋፊነት የራቀ በአመክንዮ ነገሮችን የሚመረምር አድማጭ ያጣ በሀገሬ ጉዳይ ላይ ያገባኛል የሚል ሐቀኛ ሀገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ  ውስን ቢሆንም መኖሩ የማይካድ ነው፡፡ዛሬ ላይ ግን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የጭን-ገረድ፣የውሽማና የቅምጥ  ፖለቲካዊ ስብዕናና ማንነት ያዳበሩ ሰዎች ምድር ሆናለች፡፡
በዚህ ጥሁፍ ቀጣይ ክፍል  ከላይ በርዕሱ የተመለከትነው በቀደመው ስርዓት ነገስታትና ባላባቶች  በሀይማኖታዊ መሰረት ላይ የገነቡት  ማህበረሰባዊና ፖለቲካዊ ስብዕናና ኢትዮጵያዊነት ከነገስታቱ ወሲባዊ ጠባይ ጋር እንዲመቻመች ያደረጉት የጭን-ገረድነት፣ውሽምነትና ቅምጥነት ዐመል በግዜ ሂደት ባህላዊ መሰረት መያዙና በተራው ማህበረሰብ ሳይቀር እንደ ትከክል ተወስዶ ተቀባይነት አግኝቶ ማህበረሰባዊ ወሲባዊ ጠባይ ለመሆን የበቃው በአዝማሪ ዜማና ግጥም ሳይቀር ባል በሚስቱ ላይ፣ሚስት በባሏ ላይ መወሸም፤በሚስት ላይ ቅምጥ ማኖር የወንድነት መገለጫ ተደርጎ ለውዳሴ የሚያበቃ መልከጥፉን በስም ይደግፉ አይነት ማህበረሰባዊ ነውር“እዚህ ጋር እኔ ነውር የሚለውን ቃል ለመግለፅ የተጠቀምኩት ድርጊቱን በመሰረታዊነት የክርስትና እምነት ተከታዩ  ማህበረሰብ ከምንም በላይ በሚያምናቸው የክርስትና መምህሮቹ ሐይማኖታዊ አስተምሮዎች  ጋር ድርጊቱ የሚጣረስና ባንድ በኩል እራሱም ነውር  ብሎ ስለሚኮንነው ነው፡፡
በሌላ በኩል የጋብቻን ቅዱስነት፣አንድ ወንድ ለአንድ ሴት መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮ፤ በአይኑ አይቶ በልቡ የተመኘ አመነዘረ የሚለውን ከአስርቱ ትዕዛዛት አንዱ የሆነውን ሀይማኖታዊ ቀኖናና  የዕምነት ድንጋጌ ጋር በፍፁም የሚቃረነው “ከዝሙት የሚቆጠረውን ኩነኔያዊ ተግባር”በባህልና  በፖለቲካዊ ትክክለኝነት ሂሳብ  ሁለት ፍፁም ሊጣጣሙና በአንድ ሐይማኖታዊ አስተምሮ የተቃኘ ስብዕና ውስጥ ተቻችለው ሊገኙ የማይችሉ፤ሁለት ፅንፍ የያዙ አመለካከቶችን አንድ ማንነት ሊቀበላቸውና ሊተገብራቸው የሚከብዱ መንታ ጠባያት እርስ በርሳቸው በሚጣሉ ማቶ ተረቶች እያስታከከ ከትውልድ ትውልድ እየተላለፈ የመጣ አበዋዊ ባህልና ሐይማኖትን የቀየጠ በሁለት ቢላ የመብላት፤ባንድ ራስ ሁለት ምላስ አመለካከት ለዛሬው የተምታታ ኢትዮጵያዊ ስብዕና፣ማንነት መሰረት ነው ባይ ነኝ፡፡እርግጠኛ ባልሆንም ስለዚህ ሀገራዊ ፖለቲካዊ ስብዕና ሌሊሳ ግርማ የሚባል ጠሀፊ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የጣፈውን መጣጥፍ ያነበብኩ ይመስለኛል፡፡
ትክክልና ስህተት ብሎ እራሱ የፈረጃቸውን ሁለት አብሮ አይሄዴ አመለካከቶችን በእኩል ተቀብሎ የሚኖር ሁለቱንም እያጣቀሰ ልቡን ለእግዘኤር ጭኑን ለሰይጣን ሚገብር፣ሰይጣንን ባደደባባይ የሚኮንንና የሚያብጠለጥል በጓዳው ሰይጣንን የሚያከብር ማህበረሰብ፣ሲያሻው ባደደባባይ ሙስናና ሙሰኞችን የሚጠየፍ፣ሌባ እጅ ከፍንጅ ያዝኩ ብሎ ተባብሮ እንደ እባብ ጭንቅል ጭንቅሉን  የሚቀጠቅጥ በሌላ በኩል እከሌ ከመንግስት ካዝና ይኼን ያህል ሚሊየን ብር ሰረቀ ሲባል እንዲህ ነው እንጂ እናቱ የወለደችው እያለ የሚያሞካሽ፤ለአፉ ሌብነትን የሚጠየፍ  በልቡና በተግባሩ ግን ሌቦችን የሚያደንቅ፣ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል እያለ ሚተርትና ስትሾም ካልበላህ ከንቱ ነህ እያለ ሚያጀግን፤ እርስ በርሱ የሚጣረስ  አንዱ ሌላውን ደግፎ ሊቆም በማይችል አመክንዬ በጎውን ከክፉው ያዳቀለ ድቅል ኢትዮጵያዊ ማንነት፣ክልስ ኢትዮጵያዊ ማንነት ውዥንብራችንን መለስ ብለን ብንቃኘው ምን ይለናል፡፡ከዚህ በመለስ አለማየሁ ገላጋይ በወሬሳ ልቦለዱ ተረታችንና የተምታታ ስብዕናችን ዋዘኝነት ጋር አዋህዶ ሊያሳየን የፈለገው ይሄንኑ መለቲፕል ፐርሰናሊቲ የተጠናወተው ጠባያችን ይመስለኛል፡፡
ይህቺን ሊንክ ከልከው https://www.facebook.com/kindeta ዘለቅ ብለው ያንብቡኝ!!... እርሶም የመውደጃ ምልክተዋን ተጭነው መውደድ- መዋደድዎን አይርሱ?! ለወዳጅዎም ግብዣ ይላኩ፡፡

Wednesday, October 14, 2015

ነፃነት! ነፃነት! ነፃነት!



ነፃነት! ነፃነት! ነፃነት!
(ሱራፌል ሐቢብ)
    ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አሳቡን በነፃነት የመግለፅ እና የመፃፍ መብቱን በአግባቡ ስለተጠቀመና የፍርሀት መንፈስን ድል ነስቶ በሀገሬ ጉዳይ አኔም ያገባኛል በሚል እሳቤ እውነትን በመያዝ የሐሰተኞችን የጉድ ከረጢት በብዕሩ ሸንቁጦ ነውራቸውን ለአደባባይ ስላበቃ ወህኒ ከተጣለ እነሆ ዛሬ (ጥቅምት 3/2008 ዓ.ም) ድፍን አንድ አመት ሞላው፤ የአምባገነኖች ስርዓት በተፈጥሮአዊ ባህሪው ብረት አንስቶ ከሚፋለመው ኃይል ይልቅ ብዕር ጨብጦ የሚሞግተውን አንድ ግለሰብ እጅግ ይፈራል ፤ይህ አንዱ የአምባገነኖች መለያ ባህሪ ነው! ምክንያቱም ብረት ያነሳውን ኃይል በብረቱ መመከት ይቻለው ይሆናል ነገር ግን የብዕረኞችን አሳብ በተሻለ አሳብ የሚሞግትበት እና የሚመክትበት አቅምና ችሎታ ስለማይኖረው ያለው አማራጭ እነርሱን ማሰር፣ ከሀገር እንዲሰደዱ ማድረግ ግፋም ካለ ማስወገድ ነው፡፡ መፃፍ ወንጀል፣ መናገር ሐጢያት፣ አሳብን በነፃነት መግለፅ' ነውር የሚሆነው ከማንአለብኝነት ከሚመነጭ የአምባገነኖች ስርዓት ውጪ ሌላ በምን ሊሆን ይችላል?

Sunday, October 4, 2015

የአይጦች ግልቢያ (Rat-Race



የዘር (የብሔር) ፖለቲካ አቀንቃኞች የአንድን ብሔር ማንነት ከሚኖርበት ቦታ (ጂኦግራፊ) ጋር ብቻ የሚያያዙበት አመለካከት አንድምታው ብልጠት የተሞላበት የፖለቲካ ጨዋታ ነው፡፡በጫወታውም የጫወታው ፈጣሪዎች ቀመራቸው ያለ ምንም እንከን ላስፈፃሚነት አስቀድመው በታጩት ዐይጦች ተግባራዊ እየሆነላቸውም ነው፡፡ 
የዚህ ፖለቲካዊ ጫወታ እሳቤም ሆነ የተጫዋቾቹ አይጦች ተግባር ሮበርት ቲ.ኪዮሳኪ የተባለው አሜሪካዊ ባለፀጋ በአለማችን ላይ ያሉ ባለፀጎችና ድሆች መካከል ያለውን ፤ ገንዘብ ባላቸውና በሌላቸው ሰዎች መካከል እየሰፋ የመጣውን ቅጥ የለሽ የሀብት ልዩነት መሰረት ላይ ያተኮረው “ ካሽ ፍሎው” የተሰኘ የሰሌዳ ላይ ጌም አሊያም “ራት ሬስ” ብሎ ከሚጠራው ጫወታ ጋር በብዙ መልኩ ይመሳሰልብኛል፡፡ 
ምክንያቱም ባንድም ሆነ በሌላ መልኩ ከኢህአዴግ ጋር ባንድነት የተሰለፉም ሆነ በአክራሪ የዘረኝነት አመለካከታቸው በተፃራሪ ሀይልነት የተሰለፉ ግለሰቦችም ሆነ ቡድኖች የዚህ የአይጦች ግልቢያ ውድድር ጫወታ አካል ናቸው፡፡ለዚህ ክፋት ወለድ ፖለቲካዊ እሳቤ ጠንሳሾች ሁለቱም አካላት የስውር ተልዕኳቸው ማስፈፀሚያ ወርቃማ አጋሰሶች ናቸው፡፡ለዚህ ቀመር ፈጣሪዎች የሁለቱም ወገን ጫፍ የያዘ የጋሪ ፈረሳዊ የአንድ መስመርተኝነት ጭፍን አመለካከታቸው ለኳስ አበደች ጫወታው ማድመቂያ ፤ ደጋፊውም ሆነ ተቃዋሚውም እኩል አስፈላጊና የሆኑበት ለተግባራዊነቱ ያላቸው ሚና ተመጣጣኝ በመሆኑ ነው፡፡በሁለቱ አይጦች መካከል ያለው ልዩነት የስርዓቱ ተጠቃሚ የመሆንና ያለመሆን ጉዳይ ብቻ ነው፡፡ 
ደጋፊና ተቃዋሚ አይጦች ለዓላማው ማስፈፀሚያ መሳሪያ ከመሆናቸውም በላይ፣አንዱን ብሔር ከሌላው ብሔር ጋር የጎሪጥ እንዲተያይ የጥላቻ ዘር በመዝራት እርስ በርስ በማናከስ ሁለቱም የቤንዚንነት ሚናቸውን በተገቢው መልኩ እየተወጡ በመሆኑ ለስርዓቱ መደላደያ ምቹ መደብ ሆነዋል፡፡ የዚህ ክፋት ወለድ ፖለቲካዊ እሳቤ ጠንሳሾች የስልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም፤ በዚህ እንካሰላምቲያ መሀል የራሳቸውን ወገን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና የበላይነት ለማረጋገጥ በተለያዩ መስኮች በደህንነት መረብ፣በተለያዩ ትምህርት መስኮች ዕውቀታቸውን እያጎለበቱ፣በቴክኖሎጂ፣በመከላከያ ሐይል ግንባታ ወገናቸውን እያበቁ የማይነቀነቅ የአንድ ብሔር የበላይነት የነገሰበት ሰርዓት ለመገንባት እንዲያስችላቸው አይጦቹን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንደ ፈለጉት ይጋልቧቸዋል ያስጋልቧቸዋል፡፡ 
አይጦቹም በደመነፍስ ይጋልባሉ ሌላውን ንቃተ ህሊና የጎደለውን የማህበረሰብ ክፍል ማዘናጊያነት፣ ለግዜ መግዢያ ታክቲክነት በተቀመመላቸው መርዝ እራሳቸው ተመርዘው በዕውቀት ማነስ ዘአሊያም በጥቅም ተገዝቶ የሚከተላቸውን ተከታይ በመመረዝ ሀገራዊ የፖለቲካ መስመር ተፈላጊው አንድ ቅኝታዊ አመለካከት ሰለባ እየሆነ እንዲመጣ በሀገርቤት ባለውም ሆነ ዲያስፖራ ተብዬቀዎቹ ጋር የሚንፀባረቀው ሰሞንኛው የአይጦቹ ሁለት ጎራ የለየ የዘረኝነት መንፈስ ምስክር ነው ፡፡ 
ከአፄው ስርዓት ይዞ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ፊት አውራሪነት ይቀነቀን የነበረው የብሔር እኩልነት ጥያቄ በተሳሳተ አመለካከት ላይ እንዲገነባ፣ባለፉት ስርዓት በርግጥም ግፍ የተዋለበትን የማህበረ ሰብ ክፍል ራስህን በራስህ የማስዳደር መብት ህገ መንግስቱ አውርሶሀል በሚል ሽንገላ ከራሳቸው ጥቅም ባሻገር ለወገናቸው ህልውና ግድ የሌላቸው ሆድ አደሮችን በማቀፍ በጅ አዙር ብዙሃንን ለመርገጥና ለመጨቇን እንዲያስችል ታስቦ በሸረኞች የተቀነባበረው የፖለቲካ ጫወታ ግዜ እየጠበቀ፤ መልክና ቅርፁን እየቀየረ የሚፈነዳ ቦንብ መሆኑን እያየን ነው፡፡ዛሬ ልንክደው ልንሸፍነው በማንችለው ስፋትና መጠን ከአንድነታችን ይልቅ ልዩነታችንን እንደ ዳዊት እንድንደግም እያደረገ ያለ
የክፉዎች ክፉ ዘር ነው ፡፡ 
ለዚህም ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣበት ግዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የልዩነትና ህበረት ማጣት መንስዔ፤የአንድ ብሔርተኝነት ፖለቲካዊ አጀንዳ በመሆን የለውጥ እንቅፋት ከመሆኑም በላይ በአርሶ አደሩ፣በአርብቶ አደሩ መካከል በድንበርና መሬት በተለያዩ ግዜያት የተነሱ ግጭቶች አንስቶ እስከ ፊደላውያኑ ፅንፍ ዘመምተኛ የዘረኝነት ፖለቲካ አቀንቃኞች የቃላት ጦርነት ሳይገደብ እስከ ትጥቅ ትግል መድረሱ፣በተለያዩ ወቅቶች ዩነቨርሲቲ በዘለቁ ተማሪዎች ተቃውሞና አመፅ እየታጀበ፣በተለያዩ ጎሳዎች እርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እንዲገቡ ያደረገና እዚህም እዚያም እልቂት ያስከተለ የግፈኞች ድምፅ የሌለው መሳሪያ ነበርም እንደሆነም ይቀጥላል ዘረኝነትና የዘር ፖለቲካ፡፡የሰሞኑ የአዲስ አበባን የማስፋፊያ ማስተር ፕላን ተከትሎ በማህበራዊ ድህረ ገፆች የምንመለከተው ምልልስና ሁለት ጎራ የለየ ስሜት መራሽ አተካሮ የዘረኝነትና ጠባብነት ልካችን የት ጋር እንደ ደረሰ የሚያሳይ አሊያም አውቀንም ሆነ ሳናውቅ የፖለቲካ ጫወታው ቀመር አስፈፃሚነት አይጣዊ ሚናችን ለመወጣት ደፋ ቀና እያልን ይሆንን?!... የሚያስብል ነው፡፡

ጦማር ፫



ቀን፡- መስከረም 23፣ 2007ዓ.ም
ጦማር ፫

ቢደርስም፤ባይደርስም ለተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ


ከ፡-ሱራፌል ሐቢብ

 
      የጦማር ወግ አጀማመር ደህንነትን መጠየቅ ቢሆንም የእርስዎን ደህንነት መጠየቅ ሌሎች ደህንነታቸው ሊጠየቅ የሚገባ ሰዎች ላይ አንደማሾፍ ሰለሚቆጠርብኝና በእርስዎ ደህንነትም ላይ ስጋት ስለሌለኝ ደህንነትዎን በመጠየቅ ዝባዝነኬ አላበዛብዎትም፤ አርስዎ ምን ይሆናሉ? አኛ ነን አንጂ በኑሮ ውድነት፣በፍትህ እጦት፣ በሰብአዊ መብት ጥሰት እና በአሳብ መከልከል የምንገላታ!!
      ከዚህ በፊት በላኩልዎ ሁለት ጦማሮች ባለፈው ምርጫ ፓርቲዎ በከፍተኛ ችከላ 100% በማግኘት ፓርላማውን የማህበራችሁ የግል ርስት ማድረጉ አጅግ አስነዋሪ ስራ (እንደውም ሴራ ቢባል የተሻለ ነው) መሆኑንና ተቀባይነት የሌለው ድርጊት አንደሆነ አበክሬ ገልጬልዎታለው፡፡ ክቡርነትዎ፡- እናም በዚህ የማህበራችሁ ነፃ ርስት ላይ አንድ ዓይነት የአሳብ ዘር ለመዝራት እርሻውን  በነገው እለት ማለትም መስከረም 24/2008 ዓ.ም  በይፋ አስቀድሞ  ሁለቱን  በሬዎች(አፈጉባዬዎቹን)  በመጥመድ አስከትሎም ለይስሙላም ቢሆን አርስዎን አንደዋነኛ አራሽ አድርጎ ለመሾም የሰዓታት አድሜ ነው የቀረው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡-  አስከዛሬ ድረስ ፓርቲያችሁ መንግሰት ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ሊቀመንበሩን መራሔ መንግሰት አደርጎ የመሾም ታሪኩ ተቀይሮ ስለማያውቅ አርስዎም የቀጣይ ዘመናት መራሔ መንግሰትነትዎ ለርግጠኝነት በተጠጋ ግምት  ረግቶ የሚቆይ መስሎ ስለተሰማኝ ነው  “ዋነኛ አራሽ” ይሆናሉ ብዬ ማለቴ ፡፡

      ክቡርነትዎ፡- መቼም ካልናቁኝ አንድ ምክር ልምከርዎ፤ ባለፈው ጠቅላላ ጉባዬችሁ ማብቂያ ላይ ለቀጣይ ጉባኤ ከሁለት ዓመት በኋላ አዋሳ ላይ እንገናኝ ተባብላችሁ ነው አሉ የተለያያችሁት፤ ይህ ትልቅ ስህተት አንደሆነ ግን ዳግም መገምገም ይኖርባችዋል! ለምን ቢሉ? ለብቻችሁ በያዘችሁት ርስት በፓርላማው ላይ ማከናወን የምትችሉትን ትንሽ ጉዳይ  ለምን በመንከራትት  ታገዝፉታላችሁ?! አርስዎም ቢሆኑ የመንግሰትዎ ስራ ብዙ ነው፣ ስራ ይበዛብዎታል፤ አንደው  አግረ መንገድዎን  ዘመዶችዎን  ለመጠየቅ ካላሰቡ በቀር አዋሳ ድረስ ሔደው ለምን ጊዜዎን ያባክናሉ  እዛው ከቢሮዎ በሁለት አርምጃ በማይርቀው ርስት ፓርላማችሁ ውስጥ መሰብሰቡ አይሻልም ይላሉ? አመኑኝ ለእርስዎም ሆነ ለስብስባችሁ የተሻለ አማራጭ ነው! ማን አለባችሁ? በሙላ አናንተው ናችሁ!!! ምን የሚያሰጋ ነገር አለ ብለው ነው?  ሕዝቡ ምን ይለናል ብላችሁ ከሆነ፤ ሕዝቡ ምንም አይልም! አራሱ አይደል እንዴ 100% የመረጣችሁ? ደግሞም በኑሮው ስንት አሳብ አለበት መሰልዎ፤ ስብሰባችሁ የፓርላማ መደበኛ ጉባኤ ይሁን ወላ  የፓርቲያችሁ ጠቅላላ ጉባኤ ግድም አይሰጠው፤ እናም “ይድላሽ ተንቧቺበት”  አንዳለው ዘፋኝ የአሻችሁን ታረጉ ዘንድ ሕዝቡ የፈቀደ ይመስለኛል፤ ስለዚህ ይህ ምክሬን ጣል አርገው ባያልፉ የሚሻል ይመስለኛል፤ የግድ እርስዎን ለማማከር የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ካባ ለብሼ፣ ኅሊናዬን ሽጬና ከርሴን አስፍቼ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ አማካሪ ተብዬ መሾም አለብኝ?!       
      ክቡርነትዎ፡- የርስታችሁ መናብረት በማህበራችሁ አባላት የተሞላ ቢሆንም፤ የስርአቱን አፋኝነት፣ የፖሊሲ ጥመት እና ቀሽም ሀገር የማስተዳደር ብቃት ባላቸው የእውቀት መጠን የሚተቹና፣ በሰላና በበሰለ ብዕራቸው ቁልጭ አርገው ለሕዝቡ የሚያሳዩ ብዙ የፖለቲካ ፀሐፍት በአካል ከርስታችሁ ወንበር ላይ ባይቀመጡም  በየቦታው ባለ መቀመጫቸው እንዳሉ ግን አይዘንጉ፤ ዳሩ! ክቡርነትዎ ቢዘነጉም ሆነ ቢያስተውሉ ምን ዋጋ አለው?! ደህንነትዎችዎ የፀሐፊያኑን እጅ ብዕር አስጥለው በካቴና ይጠፈንጉልዎታል፤  ምን ተዳዎ አርስዎማ!!! ግና የያገባኛል መንፈስ ፍሬ እያፈራ ለመሆኑ አመሰክርልዎታለው!!!
ክቡር ጠቅላይ ሚኒሰትር፡- በመጨረሻም  ዳግም  መራሔ መንግሰት  ሆነው የመሾም እድልዎ ከበፊት የድርጅትዎ ታሪክ መነሻነት አይቀሬ ነው ብዬ አንደምገምት ከላይ ገልፄልዎታለሁ፤ እናም ሹመት ያዳብር አንዳልልዎ ከዚህ በላይ የዳበረ እና የደለበ ሹመት የለምና ተገቢ አይመስለኝም፤ በዛ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ መሆንዎም ድራቢ መሆኑን አይርሱ፤ እነእንትና አርስዎን ከፊት አቁመው ከጀርባ ስራቸውን ይሰራሉ፤ ሴራቸውንም ያሴራሉ ፤ ሆነም ቀረ እኔም ካለሁበት 548 መቀመጫዬ ላይ ሆኜ በሀገሬ ጉዳይ ላይ  ልትውስኑ የሚገባውን ሁሉ አየተከታተልኩ ውጤት አልባ ድምፄን አጮሀለሁ!  አስከዚያው ለራሴ ስላምንና ጤናን አየተመኘሁ!! ዳግም ሰፋ ባለ ጉዳይ አሰክፅፍልዎ ደህና ልሁን!!!!