Sunday, August 16, 2015

"ግጥም እንደ አልጌ ሲፋቅ ጭረት አለው"

ሀያሲ አብደላ እዝራ:-
ዛሬ ቅዳሜ ነው! በዚህች ቀን በርካታ አስደሳች የህይወት አጋጣሚዎች አልፈዋል:: ካለፉት ጊዜያቶች ሁሉ ደግሞ የዛሬ ልዩ ነው፡፡ ለብዙ ዓመታት ደንበኛ በሆንኳትና በምወዳት አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በስነፅሁፍ ህይወቴ ለራሴ ክብር የሰጠሁበትና ወደፊት ጠንክሬ እንድፅፍ ምርኩዝ የሆነኝ አስተያየት በአካልም ሆነ በመልክ የማላውቀው ሀገራችን በኪነጥበብ ዘርፍ ካፈራቻቸውና በስነ ፅሁፍና ግጥም ዙርያ ጠንካራ ሂስ በመስጠት የሚታወቁት ሀያሲ አብደላ እዝራ እጅ የግጥም መፅሀፌ ገብታ ከፍተኛ ትኩረት አግኝታ ተገምግማ ለወደፊት ስራዬ የሚያስፈነጥረኝን እርካብ እንደመርገጥ ምን የሚያስደስት ነገር አለ?!::
እኚሁ ሀያሲ ማክሰኞ ነሀሴ 12/2007 ዓም በፑሽኪን አዳራሽ ከምሽቱ 11 ጀምሮ በተሰናዳው የመፅሀፍየምረቃ ዝግጅት ላይም እንደዚህ ቀልባቸውን ስለሳበችው መፅሀፍ ከዚህ ለየት ያለ ሙያዊ አስተያየት ሊያቀርቡ ፕሮግራም ተይዞላቸዋል፡፡ እኔም እኚህን ሰው እኩል ከናንተ ጋር ለማየት ጓጉቻለሁ፡፡
የዛ ሰው ይበለን
መልካም ቅዳሜ

0 comments